40ኛው የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ ጥቅምት 26/2015 ዓ,ም በኢትዮጵያ ሆቴል ተካሄደ

አዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌደሬሽን, 40ኛው የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ ጥቅምት 26/2015ዓ,ም በኢትዮጵያ ሆቴል ተካሄደ

40ኛው የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ

አዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌደሬሽን, 40ኛው የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ ጥቅምት 26/2015ዓ,ም በኢትዮጵያ ሆቴል ተካሄደ።

በጉባኤውም የክብር እንግዳ  በመሆን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን  ፕሬዝዳንት:የስራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ አባላት እና የፅ/ቤት ተወካይና ሌሎች የሥራ ባልደረቦች የተገኙ ሲሆን በጉባኤውም የ2014 አጠቃላይ የፌዴሬሽኑ የስራ አፈፃፀም የኦዲት ሪፖርት የ2015ዓ,ም እቅድ እና የፌዴሬሽኑ የክፍያ ተመን ለውይይት ቀርቦ  ተሣታፊው አሥተያየት ሠጥቶበት በማፅደቅ ፌዴሬሽኑ ለስፖርቱ  ማህበረሠብ  መረጃን  ተደራሽ  ለማድረስ የሚረዳን  ድህረ -ገፅ በመክፈት ያሥመረቅን ሢሆን  በተጨማሪም በ2014ዓ,ም ክለቦች ባደረጉት ተሣትፎ

  1. ከ1ኛ ዲቪዝዮን
    1ኛ, የመቻል ክለብ 50,000ብር
    2ኛ, የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች 40,000ብር
    3ኛ, የኢ/ንግድ ባንክ   30,000ብር
  2. ከ2ኛዲቪዝዮን
    1ኛ አዲስ አበባ ፖሊስ 40 ,000   ብር
    2ኛ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 30,000ብር
    3ኛ አራዳ ክ/ከተማ            20,000ብር
    3ኛ ኤልሚ ኦላንዶ             20,000ብር የተሸለሙ ሢሆን
  3. ከአንደኛ ዲቪዝዮን  ባገኙት  ውጤት ወደ  ሁለተኛ ዲቪዝዮን በ2013ያደጉ
    ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ  20,000ብር
    ኢኮስኮ                         20,000ብር

በ2014 ከ2ኛ ዲቪዝዮን ወደ አንደኛ ዲቪዝዮን ላደገ ለአ/አ /ዩኒቨርስቲ 20,000ብር ድጋፍ  ተሠጥቶአቸዋል። ክ/ከተሞች ክለብ ከማቋቋም አንፃር በፍጥነት ተደራጅቶ  ክለብ ላቋቋመው  ለለሚ  ኩራ ክ/ከተማ  የሞሥጋና  ሠርተፍኬት  ተበርክቶለታል  በተጨማሪም   በፌዴሬሽኑ ሥር  ተመዝግበው ለሚገኙ 3 ማህበራት:-
1, የአዲስ አበባ አንጋፋ አትሌቶች ማህበር 30,000ብር
2, የአሠልጣኞች ማህበር 30,0000ብር
3, የዳኞች ማህበር  30,000 ብር ድጋፍ የተደረገላቸው መሆኑና  ፌዴሬሽኑን ለብዙ አመታት ያገለገሉና  ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላደረጉ የሽልማትና የሠርተፍኬት ሥጦታ በመሥጠት ባማረና በደመቀ ሁኔታ ጉባኤው ተጠናቆዋል::

አዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌደሬሽን

moha-soft-drinks-industry