በአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የሚደገፉ የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት

የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ያደረገለትን ትጥቅ ድጋፍ ለታዳጊ ወጣቶች ወላጆች በተገኙበት የአመቱን የሥልጠና ሂደት በጋራ ከገመገመ በኋላ ለታዳጊ ወጣቶች የትጥቅ ርክክብ አድርገዋል።
በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የሚደገፍ የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት

የአዲስ አበባ ታዳጊ ወጣቶች ስልጠና ፕሮጀክት
በዚህ ፕሮጀክት ዉስጥ ከ18 እና ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊ ወጣቶች ስልጠና የሚወስዱ ሲሆን ስልጠናቸዉንም ሲያጠናቅቁ ፌዴሬሽኑ ውድድር በማድረግ ብቁ የሆኑ አትሌቶችን በመምረጥ በአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተይዘው ድጋፍና ክትትል እንዲሁም ስልጠና ይሰጣቸዋል፡፡

ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየአመቱ የስፖርት ልብስና የወተት ድጋፍ እየተሰጣቸው ከአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በጀት ሁለት አሠልጣኞችን በመቅጠር ና ለታዳጊ ወጣቶች በወር 250ብር አበል በመክፈል ክትትልና ድጋፍ የሚደረግላቸው የፕሮጀክት ሠልጣኞች ናቸዉ፡፡
በታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት ተጨማሪ ምስሎችን ለማየት ከታች ያለውን ማስፈንጠርያ ይጫኑት
የሀ-17 ታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት ሰልጠኞች በባለሙያዎች ምዘና
የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት ለአሠልጣኞች ለሥራ አሥፈፃሚ እና ለቴክኒክ ኮሚቴ የስፖርት ትጥቅ ድጋፍ